1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በአማራና ትግራይ ክልሎች ዳግም ደም አፋሳሽ ግጭት እንዳይከሰት ምን ይደረግ?

እሑድ፣ የካቲት 24 2016

የጦርነቱ ጠባሳ ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ ግድም በኋላም በጉልኅ ይታያል ። ባለፉት ሳምንታት በትግራይ እና አማራ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ ታጣቂዎች መካከል ለአጭር ጊዜያት የቆዩ ግጭቶች ከአንዴም ሁለት ጊዜ መከሰታቸው ነዋሪዎችን እጅግ አስግቷል ።

በሰሜኑ አውዳሚ ጦርነት የጋየ የወታደራዊ ተሽከርካሪ
በሰሜኑ አውዳሚ ጦርነት የጋየ የወታደራዊ ተሽከርካሪ ። ፎቶ፦ ከማኅደርምስል Million Haileselassie/DW

የሁለቱም ክልል ነዋሪዎች ከጦርነት ሰላምን ይሻሉ

This browser does not support the audio element.

የፕሪቶሪያው ስምምነት ተፈርሞ የጠመንጃ አፈሙዝ ልሣናት ይዘጉ እስከተባለበት ድረስ በተካሄደው የሰሜኑ ጦርነት የበርካታ ኢትዮጵያውያን  ሰዎች ሕይወት ተቀጥፏል ። ብዙዎች ለአካል ጉዳት ተዳርገዋል ፤ ከቤት ንብረት ከቀዬያቸውም ተፈናቅለዋል ። የጦርነቱ ጠባሳ ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ ግድም በኋላም በጉልኅ ይታያል ። ባለፉት ሳምንታት በትግራይ እና አማራ ክልሎች  ውስጥ በሚገኙ ታጣቂዎች መካከል ለአጭር ጊዜያት የቆዩ ግጭቶች ከአንዴም ሁለት ጊዜ መከሰታቸው ነዋሪዎችን እጅግ አስግቷል ።

ኹነኛ መፍትኄ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ሳይበጅለት ተድበስብሶ የቆየው የሁለቱ ክልሎች ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ የሚጠይቁ ድምፆች እየተስተጋቡ ነው ።  በሁለቱም ክልሎች በጦርነት እና ተደጋጋሚ ግጭቶች እጅግ የተጎዳው ማኅበረሰብ ለረሐብ እና ለእርዛትም ተዳርጓል ። አማራ ክልል የፋኖ እና የከመከላከያ ጦርነት ቀጥሏል ።  በዚህ ሁሉ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በአማራና ትግራይ ክልሎች  በርካታ ሕዝብ የተገደለበት አይነት ዳግም ደም አፋሳሽ ግጭት በሁለቱ ክልሎች መካከል እንዳይከሰት ምን ይደረግ? የዛሬው የእንወያይ መሰናዶዋችን ዋነኛ ትኩረት ነው ።

በውይይቱ 3 እንግዶች ተሳታፊ ናቸው።

  1. ገብረየሱስ ተክሉ ባሕታ (/) በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የኅብረተሰብ ሣይንስ እና ቋንቋዎች የኮሌጅ መምህር

  2. አቶ ባይሳ ዋቅወያ፦ የዓለም አቀፍ ሕግ ባለሞያ፤ ላለፉት 30 ዓመታት የተመድ ባለሥልጣን

  3. ሲሳይ መንግስቴ አዲሱ (/)  በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ፤ ፌዴራሊዝም እና ሰብአዊ መብቶች መምህር እና ተመራማሪ  ናቸው ።

በውይይቱ መግቢያ ላይም፦ የአማራና የትግራይ ክልሎች  የይገባኛል ጥያቄ በሚያነሱባቸው አካባቢዎች ከሚኖሩ ሰዎች ያሰባሰብናቸው አስተያየቶችም ተካቷል ። አስተያየት ሰጪዎቹ ውጥረቶች በመላ በሰላማዊ መንገድ በውይይት እንዲፈታ ጠይቀዋል ።

የጠመንጃ አፈሙዝ ልሣናት ይዘጉየተባለበት የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሲፈረምምስል Yasuyoshi Chiba/AFP/Getty Images

ሙሉ ውይይቱን በድምፅ መከታተል ይቻላል ።

«በአማራና ትግራይ ክልሎች ዳግም ደም አፋሳሽ ግጭት እንዳይከሰት»፦ በሚል ርእስ በቀረበው ውይይት ተሳታፊ እንዲሆኑ ለጠቅላይ ሚንስትር ጽ/ቤት በኢሜል ብንጠይቅም ለውይይቱ ተሳታፊ የሚሆን ሰው እንደሌለ በዛው በኢሜል ምላሽ ተሰጥቶናል ። ለመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር) እንዲሁም ለምክትላቸው ሠላማዊት ካሳ በዶይቸ ቬለ በኩል የላክነው ይፋዊ የኢሜል ግብዣ ውይይቱን እስካደረግንበት ጊዜ ድረስ ምላሽ አላገኘም ።

ሙሉ ውይይቱን በድምፅ መከታተል ይቻላል ።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ኂሩት መለሠ

 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW