1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የትንሳኤ በዓል አከባበር በኦርቶዶክስ እና ካቶሊክ አብያተ ክርስቲያናት 

እሑድ፣ ሚያዝያ 16 2014

በአዲስ አበባ በሚገኙት ሰዓሊተ ምህረት የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና የቅዱስ ዮሴፍ ካቶሊክ ቤተክርስትያን ካህናት ከቅዳሜ ምሽት ሥርዓተ ቅዳሴ ሲከወን፣ ጸሎት እና ምሥጋና ሲደረግ የዶይቼ ቬለ ዘጋቢ ተገኝቶ ነበር።

Äthiopien Addis Abeba | Messe Katholische Kirche St. Joseph
ምስል Solomon Muchie/DW

የትንሳኤ በዓል አከባበር በኦርቶዶክስ እና ካቶሊክ አብያተ ክርስቲያናት 

This browser does not support the audio element.

በክርስትና እምነት አማንያን ዘንድ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ የተነሳበት የፋሲካ ወይም የትንሣኤ በዓል ዛሬ እየተከበረ ነው።

ትናንት በትንሣኤው ዋዜማ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት አብያተ ክርስትያናት በተለይም የቅዳሴ ሥነ ሥርዓት በተዋበ መንፈሳዊ ክዋኔ ከምሽቱ ሦስት እስከ ሌሊቱ አሥር ሰዓት ተፈፀማል።

አዲስ አበባ ጉድር ሾላ የሚገኘው ሰዓሊተ ምህረት ቤተ ክርስቲያን

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አዲስ አበባ ጉድር ሾላ በሚገኘው ሰዓሊተ ምህረት ቤተ ክርስቲያን እና ጎሮ አካባቢ በሚገኘው በአዲስ አበባ አገረ ስብከት የቅዱስ ዮሴፍ ካቶሊክ ቤተክርስትያን የዋዜማው ምሽት እና ሌሊት ድምቀት በተሞላው መንፈሳዊ ሥርዓት ዋዜማው ትከብሯል።

ሰለሞን ሙጬ
እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW